የኢንተርኔት እና የዳታ ስርጭት ኢትዮጵያ ውስጥ አሁንም ተደራሽነት ይጎለዋል። ይሄንን ችግር ለመቋቋም እና የዲጂታል ትምህርትን ለሁሉም ለማድረስ በሌላ አይነት ቴክኖሎጂ እንጠቀማለን።
ትናንሽ ሰርቨርዎችን በተለያዩ ትምህርት ቤትዎች እና ተማሪዎች በሚገኙባቸው ቦታዎች በመግጠም ትምህርታችን ያለ ምንም ኢንተርኔት ዳውንሎድ እንዲደረግ ያስችላል። እነዚህ ሰርቨርዎች አጠቃቀማቸው ቀላል እና በቀላሉ የማይበላሹ ናቸው።